የልደታ ክ/ከተማ ዳግም ህዳሴ ጤና ጣቢያ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ተሰጥተውታል

  1. የሀገሪቱን የጤና ፖሊሲና ደረጃ በማገናዘብ የጤና ጉዳዮች ላይ የግንዛቤ ማስፋፊያ ትምህርት ለነዋሪው አመቺ በሆነ ዘዴ ይሰጣል ወይም እንዲሰጥ ያደርጋል፤
  2. አጠቃላይ የሆነ የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥርና ቅኝት ያደርጋል፤ ይቆጣጠራል፤ ይከላከላል፤ መረጃዎችን ያሰባስባል፤ ወረርሽኝ ሲነሳ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ይከላከላል፤
  3. የእናቶችና ህፃናት ጤና ክብካቤ አገልግሎት ይሰጣል ወይም እንዲሰጥ ያደርጋል፤ ይቆጣጠራል፤
  4. ከፌደራል መንግሥት እና ከዕርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ለተለያዩ ፕሮግራሞች ማስፈጸሚያ የሚሰጡ መድኃኒቶችንና የሕክምና መሳሪያዎችን ያሰራጫል፤ ስራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላል፤ ይቆጣጠራል፤
  5. የጤና አገልግሎት ፕሮግራሞችን ከሚያካሂዱ መንግሥታዊ ያልሆኑ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጋር ሕጋዊ ስምምነቶችና ውሎች ይፈጽማል፤ አፈጻጸማቸውን ይከታተላል፤
  6. በተቋሙ ውስጥ የሚከናወኑ የኤች አይ ቪ/ ኤድስና ሌሎች በሽታዎች ቁጥጥር መረጃ ያጠናቅራል፤ በአግባቡ በመተንተን ለሚመለከተው ሪፖርት ያደርጋል፤
  7. የጤና አጠባበቅ የምክርና የመረጃ አገልግሎት ያደራጃል፤ ይሰጣል፤